ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ በኦሮሚያ ክልል አጋርሳ ወረዳ የስንዴ ማሳን ጎበኙ

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ

ግንቦት 27/2013 (ዋልታ) – ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ጋር በመሆን በክልሉ አጋርሳ ወረዳ በ30 ሄክታር መሬት በመልማት ላይ ያለውን የስንዴ ማሳ ጎብኝተዋል።

የስንዴ ማሳው ስፒሪንክለር በተባለ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመልማት ላይ መሆኑን ከቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።