ወቅቱ ከትርፍ በላይ ሀገር እና ህዝብ ስለማትረፍ የምናስብበት ነው ተባለ

ነሃሴ15/2013(ዋልታ) – ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የኑሮ ውድነት ለማሻሻል የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ በከተማዋ ካሉ የንግዱ ማህበረሰቦች ጋር ወይይት እያካሄዱ ነው፡፡

በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት ተገኘተዋል፡፡

የኑሮ ውድነቱን ለማሻሻል ከንግዱ ማህበረሰብ ምን ይጠበቃል ፣ መንግስትስ መውሰድ ያለበት እርምጃ ምን መሆን አለበት በሚለው ላይ ነው ሰፊ  ውይይት እየተካሄደ ነው  የሚገኘው ።

ሀገርን ለማዳን የህልውና ዘመቻ ላይ እንደመሆናችን የንግዱ ማኅበረሰብ በዚህ ከባድ ወቅት ከትርፍ ይልቅ ለሀገር እና ለህዝብ ቅድሚያ  ሊሰጡ ይገባል ተብሏል ፡፡

(በሜሮን መስፍን)