ምክር ቤቱ የ16 አዳዲስ የካቢኔ አባላት ሹመትን አፀደቀ

የህዝብ  ተወካዮች  ምክርቤት በዛሬ ዕለት  ባካሄደው  የ3ኛው ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ  በጠቅላይ  ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ በእጩነት  የቀረቡትን  የ16 የካቢኔ አባላትን  ሹመት  በሙሉ ድምጽ  አፀደቀ ።

ጠቅላይ  ሚንስትር ዶክተር አብይ የካቢኔ ሹመቱን ሲያቀርቡ እንደገለጹት ህዝቡ የሚያነሳውን  ሰላም፣ ልማትና የዴሞክራሲ ጥያቄ በብቃት ለመመለስ ለውጥ ማምጣት አስፈላጊ መሆኑ  ታምኖበት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል ።

በአዲሱ  የካቢኔ ሹመት የቀረቡት  እጩዎች  ብቃትን ፣ ልምድና የትምህርት ዝግጅትን እንዲሁም  ያለፈውን  የሥራ አፈጻጻም  መሠረት  በማድረግ  የተመረጡ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል ።

በአዲስ በተደራጀው  ካቤኔም የሴቶች ተሳትፎም  50  በመቶ  እንዲሆን በመደረጉ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካም የመጀመሪያ መሆኑን  ጠቅላይ ሚንስትሩ  አስረድተዋል ።

አዲስ  የካቢኔ አባላት  ሌብነትን የሚጠየፉ፣ ሃብት የማያባክንና ቅንንነት የተሞላበትን አገልግሎት  የሚሠጡ መሆን  ይጠበቅባቸዋል ብለዋል ጠቅላይ ሚንስትሩ ።

በቀጣይ   የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት   የተሾሙ  አዲስ  የካቢኔ አባላት አፈጻጸምን በመከታተልና  በመቆጣጣር በኩሉ  የበኩላቸውን   ሚና እንዲጫወቱ  ጠቅላይ ሚንስትሩ ጥሪ አቅርበዋል  ።

የአራት  የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ሚንስትሮች  ባሉበት እንዲቀጥሉም መደረጉ ጠቅላይ ሚንስትሩ ገልጸዋል ። 

 

አዲሱ  የካቤኒ አባላት ሹመት ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል    

  1. ወይዘሮ  ሙፈሪያት ካሚል  የሰላም ሚኒስትር   
  2. ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረግዛብሔር – የንግድና ኢንዱስትሪ ሚንስትር
  3.  ኢንጂነር አይሻ መሐመድ- የአገር መከላከያ ሚኒስትር  
  4. አቶ አህመድ ሽዴ- የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስትር
  5. አቶ ኡመር ሁሴን – የግብርና ሚኒስትር
  6. ወይዘሮ  አዳነች  አቤቤ -የገቢዎች ሚኒስትር
  7. ዶ/ር ኦርጌጌ ተስፋዬ – የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር
  8. ዶ/ር ፍጹም  አሰፋ  – የፕላንና የልማት ሚኒስትር
  9. ዶ/ር ሂሩት  ወልደማሪያም – የሳይንስና  ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር
  10. ዶ/ር ጥላዬ ጌቴ- የትምህርት ሚኒስትር
  11. ወይዘሪት የዓለም ፀሃይ ፀጋዬ- የሴቶች ፣ ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስትር  
  12. ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ -የትራንስፖርት ሚኒስትር
  13. ዶ/ር ጌታሁን መኩሪያ – የኢኖቭዬሽንና ቴክኖሎጂ ሚነስትር
  14. ዣንጥራር አባይ -የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር
  15. ዶ/ር ሳሙኤል ሆርኮ- የማዕድንና የነዳጅ ሚኒስትር  
  16. ዶ/ር ሂሩት  ካሳው – የባህልና ቱሪዝም  ሚኒስትር  ናቸው  ።