ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዛሬው ዕለት ለአራት የፌደራል መንግስት የስራ ኃላፊዎች ሹመት ሰጡ።
በዚሁ መሰረት፤
1. አቶ ብናልፍ አንዱዓለም – በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና አስተባባሪ
2. አቶ መለስ ዓለሙ – በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ምክትል ዋና አስተባባሪ
3. አቶ ተመስገን ጥሩነህ – የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር
4. አቶ ደሴ ዳልኬ – በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግብርና እና የመስኖ አማካሪ በመሆን ከጥቅምት 7 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ ተሾመዋል።
የተሰጠው ሹመት የትምህርት ዝግጅትና የፖለቲካ አመራር ብቃትን ከግምት ያስገባ መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።