ሴቶች በሰላምና በግጭት አፈታት ላይ ያላቸውን ሚና ለማጎልበት የተጠናከረ ሥራ መሥራት እንደሚገባቸው ተገለጸ

ሴቶች በሰላምና በግጭት አፈታት ላይ ያላቸውን ሚና ለማጎልበት የተጠናከረ ሥራ  መሥራት እንደሚገባቸው በዛሬው ዕለት በህዝብ ተወካዮች  ምክር ቤት በተካሄደው ውይይት ተገለጸ ።

የሰላም ሚኒስቴርና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጋራ ሆነው ባዘጋጁት የሴት አፈጉባኤዎች  መድረክ  ላይ እንደተገለጸው ሴቶች በአገሪቱ ሰላምና ግጭት አፈታት ላይ ያላቸውን ሚና ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚሠሩ ገልጸዋል ።

በውይይት መድረኩ ላይ በዘጠኝ ክልሎች፣በሁለት ከተሞች ከወረዳ እስከ  ክልልና ከተማ ምክር ቤቶች  ውስጥ  እያገለገሉ የሚገኙ  አፈጉባኤዎች  ተገኝተዋል ።

ሴቶች ግጭትን በመፍታት ረገድና የሰላም እሴትን በመገንባት ረገድ ያላቸውን መሪ ሚና እንዴት ማሳደግ እንዳለባቸው  የሚያሳይ   ጥናታዊ ጽሑፍ  በወይዘሮ ሙባ መሐመድ ቀርቧል ።

ሴት አፈጉባኤዎችን ያሳተፈው ይህ  ጉባኤ  “ ሴት አፈጉባኤዎች ለሰላም”  በሚል  መሪ ቃል ነው  የተካሄደው ።

በመድረኩ ላይ  የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አፈጉባኤ  ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ፣ የፌደሬሽን  ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ኬሪያድ ኢብራሂም  ተገኝተዋል ።