ሮበርት ሙጋቤ ከሥልጣናቸው በፍቃዳቸው ለቀቁ

ፕሬዚደንት ሮበርት  ሙጋቤ  ትናንት  በፍቃዳቸው ከሥልጣን  ለቀቁ  ።

የፕሬዚደንት ሮበርት ሙጋቤ ከሥልጣን መልቀቅን  ተከትሎም   በተለያዩ  የአገሪቱ  ክፍሎች  የሚገኙ  ዚምባቤያውያን ትናንት  ምሽት ደስታቸውን  ሲገልጹ ታይተዋል  ።    

አንድ  ዚምባብያዊ  እንደገለጸው  ሙጋቤ  ለ37 ዓመት በሥልጣን  ቆይቷል እግዚአብሔር  ብቻ ነው አሱን  ማንሳት  የሚችለው  ብሏል  ።  

አንዳንድ  አፍሪካውያን  ሮበርት ሙጋቤ  የአፍሪካ ነጻነት  ጀግና  መሆኑን  እየገለጹ ሲሆን  ሌሎች  ደግሞ  ሙጋቤ አምባገነን መሪና  የዚምባብዌን ኢኮኖሚ ከጥቅም  ውጭ  ያደረገ  መሆኑን   ይናገራሉ ።      

በትናንትናው ዕለት በተካሄደው የዚምባብዌ ፓርላማ ስብሰባ ላይ የፓርላማው አፈጉባኤ ከሮበርት ሙጋቤ የተጻፈውን  የሥልጣን  መልቀቂያ   ደብዳቤ  በፓርላማው ተነቧል  ።    

ሙጋቤ  በጻፉት የሥልጣን መልቀቂያ ደብዳቤ ላይ እንደገለጹት ከህዝቡ በመጣው ግፊት ፣ የዚምባብዌ ሠራዊትና  የገዥው ፓርቲ ባሳደሩት ጫና  ምክንያትና  በአገሪቱ  ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር እንዲኖር  ለማስቻል  በፍቃደኝነት  ከሥልጣናቸው መልቀቃቸው  አስታውቀዋል ሙጋቤ ።   

የዚምባብዌ ገዥ ፓርቲ ዛኑ  ፒኤፍ  የህግ አውጪ የሆኑና የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት  በዚምባብዌ መልቀቅ የተሰማቸው  የደስታ ስሜት  በፓርላማው  የገለጹ ሲሆን  ዚምባብያውያን በሙጋቤ  መልቀቅ ምክንያት በየመንገዱ   የዳንስ ፣  የዘፈን ፣ የፈንጠዝያ ጭፈራቸውን ትናንት  ምሽት  ሲያሳዩ ታይተዋል  ።        

ጁሊያን ምቱኩዲዚ ለኤፍፒ የዜና ወኪል እንደተናገረው በሙጋቤ ከሥልጣን መልቀቅ እጅግ መደሰቱንና ይህ ወቅት  ለዚምባብዌ እጅግ ወሳኝ  መሆኑን ገልጿል ።

እስካሁን በዚምባብዌ  እየተፈጠረ  ባለው ሁኔታ  እንቅልፍ አጥተን ቆይተናል ያለው ምቱኩዲዚ  አሁን ፍላጎታችብ በመሳካቱ  ደስታው  የላቀ  መሆኑብ  ለቢቢሲም አክሎ ገልጿል ።(ምንጭ : ቢቢሲ)