ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከቡና ፣የቅመማቅመምና የሻይ ቅጠል ምርቶች 560 ሚሊየን ዶላር ተገኝቷል

በበጀት  አመቱ  ዘጠኝ   ወራት  ውስጥ  148 227 ነጥብ  2  ቶን   ቡና ፣ቅመማ ቅመምና   ከሻይ  ቅጠል  ምርቶች  ወደ የተለያዩ  አገራት ተልከው 560 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ማግኘት  መቻሉን  የኢትዮጵያ  ቡናና  ሻይ  ልማትና   ግብይት   ባለስልጣን  አስታወቀ፡፡ 

የባለስልጣኑ  የገበያ   ልማትና   ፕሮሞሽን    ዳይሬክተር   አቶ   ዳሳ ዳኒሶ   እንደተናገሩት  ባለስልጣኑ  170 354 ነጥብ 72  ቶን  በመላክ  649 ሚሊየን   ዶላር  ለማግኝት አቅዶ ነበር፡፡

ባለስልጣኑ ካቀደው  በመጠን 85.55  በመቶው ከገቢ ደግሞ 86.3 በመቶውን  ማሳካት  ችሏል፡፡

አፈጻጸሙ   ከባለፈው  ዓመት   ተመሳሳይ  ወቅት   ጋር   ሲነጻጸር   በመጠን  4.5%  በገቢ 15%  ጭማሪ   ማሳየቱም  ተገልጿል፡፡ 

ወደ  ውጭ   ከተላከ   139 887  ቶን   የቡና  ምርት  ብቻ  545 ሚሊየን    ዶላር  ገቢ  ማግኘት   መቻሉን  የገለጹት  ዳይሬክተሩ  የእቅዱን   በመጠን  88.12 %   በገቢ 87.91 %  መሳካት  መቻሉን   ተናግረዋል፡፡

ባለስልጣኑ  በበጀት   አመቱ   241    ቶን  ቡና  ወደ  ውጭ   በመላክ  941 ሚሊየን  የአሜሪካን  ዶላር  አቅዶ  እየሰራ መሆኑም   ታውቋል፡፡

በቀሪዎቹ  ሶስት ወራት  የቡና ምርት  ለገበያ   የተሻለ  የሚቀርብበት በመሆኑ  የዓመቱን  እቅድ   ለማሳካት እንደሚቻልም  ተመላክቷል ( ኢዜአ)