የአዋላጅ ነርሶች ቁጥር ማነስ ለአገልግሎት ጥራት ማነስ ምክንያት እየሆነ መምጣቱ ተገለጸ

የአዋላጅ ነርሶች ቁጥር ማነስ ለአገልግሎት ጥራት ማነስ ምክንያት እየሆነ መምጣቱን የኢትዮጵያ ሚድዋይፈሮች ማህበር  አስታወቀ ።

የእናቶችና ህጻናት ሞትን  ለመቀነስ የአዋላጅ  ነርስ ባለሙያዎች አስፈላጊነት  ከፍተኛ መሆኑን የሚጠቅሱት ባለሙያዎች አሁን እየታየ ያለው የአዋላጅ ነርስ ቁጥር ማነስ ለአገልግሎት ጥራት ችግር  እየሆነ  መምጣቱን ማህበሩ ገልጿል ።

በአሁኑ ወቅት ከአገሪቱ ህዝብ ቁጥር አኳያ ከቅድመ ወሊድ ጀምሮ ሰባት አይነት ክህሎት  ያላቸው  አዋላጅ  ነርሶችን ቁጥር ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት  ጋርም መሥራት  እንደሚያስፈልግ ተገልጿል ።  

ኢትዮጵያ አሁን ያላት የአዋላጅ ነርስ ባለሙያዎች ቁጥር ከአስራ ሁለት ሺ የማይበልጡ መሆኑን የተለያዩ የመረጃ  ምንጮች የሚገልጹ በአሁኑ ወቅት ግን አገሪቷ ሀምሳ ሺ  የሚሆኑ የአዋላጅ  ነርሶች  እንደሚያስፈልጋት  የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ ፡፡