የማህበረሰብ ጤና አገልገሎት በድህነት የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው

የማህበረሰብ ጤና አገልግሎት በአዲስ አበባ የድሃ ድሃ የሚባሉትን ወይም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ እንዳይገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው ።

የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በአመት 300 ብር የአባልነት ክፍያን ብቻ በመክፍል ነው  ዓመቱን ሙሉ ገደብ የሌለው የጤና አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ዋልታ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገልጸዋል ።

የህክምና አገልግሎቱ ከሚሰጡባቸው በአንዱ የልደታ ከፍለ ከተማ በመገኘትም የሚመለከታቸውን አካላት በማናገር በዚው ጉዳይ ተጨማሪ ዘገባ ብርሃኑ ወልደሰማያት አዘጋጅቷል ።

የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ በበኩሉ  የጤና አገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ያለባቸው ባለመብቶች ሁሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይበልጥ ሥራ  እየተሠራ መሆኑን አመልክቷል ።