ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሹመት ሰጡ

መስከረም 28/2014 (ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አቶ አብርሃም አለኸኝን በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዘርፍ አስተባባሪ እንዲሆኑ ሹመት ሰጥተዋል።
አቶ አብርሃም አለኸኝ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወቃል።