ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ በሚመራው የ‘ስማርት አፍሪካ’ ቨርቹዋል የቦርድ ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል፡፡
‘ስማርት አፍሪካ’ በአህጉሪቱ ቀጣይነት ያለው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት እንዲፋጠን በአፍሪካ መሪዎች ተነሳሽነት የተጀመረ ፣ የአፍሪካን ብሮድባንድ ተደራሽነት እና የኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዕድገትን ለማሳለጥ የተነደፈ ዕቅድ ነው፡፡
ፕሬዝዳንቷ በኢትዮጵያ የፀደቀውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂ እና የተወሰዱ እርምጃዎችን በተመለከተ ለተሰብሳቢዎች ገለፃ ማድረጋቸውን ከፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡