ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል የማይተካ ሚና አለው – ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ

ሰኔ 02/2013 (ዋልታ) – ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል በሌላ የማይተካ ሚና እንዳለው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ፡፡
የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር (ጉልባማ) ከተማ አቀፍ የምክክር መድረክ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትርሩ “ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል በሌላ የማይተካ ሚና አለው” ሲሉ በማህበራዊ የትስስር ገፃቸው አስፍረዋል፡፡
በተባበረ መንፈስ በመስራት ልማታችንን ልናረጋግጥ ይገባልም ብለዋል፡፡
በምክክር መድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ለጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር የባህል ማዕከል ግንባታ ቦታ ማስረከባቸው ታውቋል፡፡