ጥር 30/2016 (አዲስ ዋልታ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቀረበለትን የካቢኔ አባላት ሹመት በአብላጫ ድምጽ አፀደቀ።
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 15ኛ መደበኛ ስብሰባ የአስፈጻሚ አካላት ሹመት አፅድቋል።
በዚህም መሰረት፡-
- አቶ ተመስገን ጥሩነህ ….…………ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር
- አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ………የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
- ዶክተር መቅደስ ዳባ ……………….የጤና ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል፡፡