በኒው ዮርክ ለህዳሴ ግድብ ድጋፍ የሚሰጥና እና ተሟጋች ቡድን ተመሰረተ

 

|

 

የካቲት 15 ፣ 2013 (ዋልታ) – በኒው ዮርክ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ የሚሰጥ እና ተሟጋች ቡድን መመስረቱን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በቲውተር ገጻቸው ላይ ገልጸዋል።

በበየነ መረብ በተካሄደው በዚህ ቡድን ምስረታ ላይ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚንስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ መሳተፋቸው ተገልጿል።

ቡድኑ በውጭ የሚኖሩ የኢትዮጵያ የማህበረሰብ አባላት ፣የሲቪል ማህበረሰብ መሪዎች ፣ ምሁራን እና ባለሙያዎችን ያቀፈ ነው፡፡