በአዲስ አበባ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ተጀመረ

ሰኔ 19/2013 (ዋልታ) – በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጉለሌ እጽዋት ማእከል  የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር “አዲስ አበባን እናልብሳት” በሚል እየተካሄደ ነው።

መርሃግብሩን ያስጀመሩት የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አዳነች አበቤ በከተማ ደረጃ  7 ነጥብ 5 ሚሊየን ችግኝ እንደሚተከል ተናግረዋል።

የእለቱ የክብር እንግዳ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር አዲስ አበባ ለክልሎች ምሳሌ የሚሆን ሥራ እየሰራች ነው ብለዋል።

እንደ ክልልም 2 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል እየተሰራ መሆኑን አቶ አገኘሁ ተናግረዋል።

መርሀ ግብሩ ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተካሂዷል።

(በምንይሉ ደስይበለው)