ሚኒስቴሩ ለኮቪድ-19 ህሙማን የሚውሉ 20 ሺህ የቀርከሃ አልጋዎች አስረከበ

ሰኔ 19/2013 (ዋልታ) – የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ለኮቪድ-19 ህሙማን የሚውሉ 20 ሺህ የቀርከሃ አልጋዎችን ለጤና ሚኒስቴር ድጋፍ አድርጓል፡፡

የቀርከሃ አልጋዎቹ ከጀርመን ተራድኦ ድርጅት( ጂ አይ ዜድ)  በተገኘ ድጋፍ የተሰሩ ናቸው፡፡

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር  መላኩ አለበል ኮሮና ቫይረስን  በመከላከልና በመቆጣጠር ሂደት የኢትዮጵያ መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጓዳኝ  ጂ አይ ዜድ ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፐን አውር በበኩላቸው የጀርመን መንግስት በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመከላከል የሚያደርገውን ጥረት  አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳሃረላ አቡዱላሂም ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከጀርመን ተራድኦ ድርጅት ጋር በመተባበር ላከናወነው ተግባር ምስጋና እና እውቅና ሰጥተዋል፡፡

ድጋፉ የኮቪድ-19 ህሙማን ወደ ህክምና ሲገቡ ሊከሰት የሚችለውን የአልጋ እጥረት ለመቅረፍ  ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት መገለጹን ከንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡