አምባሳደር ታዬ የቱንም ያህል ጫና ቢኖር ኢትዮጵያን ለመታደግ እንሰራለን አሉ

ጥር 2/2014 (ዋልታ) የኃያልነት ከፍተኛ የፖለቲካ ጫና ቢኖርም ኢትዮጵያን ለመታደግና ዕጣ ፈንታዋን ለመወሰን የገባነውን ቃል በማክበር እንሰራለን ሲሉ በተባበሩት መንግሥታት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ገለፁ፡፡
አምባደር ታዬ አሸባሪው የትሕነግ ቡድን የፈጸመውን የጦር ወንጀሎች በተመለከተ በተለያዩ አገራት ለሚገኙ የሃይማኖት መሪዎችና በየእምነቱ ተሰሚነት ላላቸው ሰዎች በበይነ መረብ ገለፃ አድርገዋል፡፡
የኢትዮጵያን ኅልውና ለመጠበቅ እና ቀጣይነትን ለማረጋገጥ በጥበብ እና በአስተዋይነት የመጓዝን ተገቢነትም በቲውተር ገጻቸው ጽፈዋል፡፡