የካቲት 11/2013 (ዋልታ) – የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያና የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ፡፡
ስምምነቱን የተፈራረሙት ከመከላከያ የተለያዩ ክፍሎችና ከፌዴራል ፖሊስ የተውጣጡ ሙያተኞች ናቸው ተብሏል፡፡
በስነ ስርዓቱ ላይም የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሜጀር ጀነራል ጥጋቡ ይልማ እና የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር አቶ አስቻለው መገኘታቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡