የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው፡፡

ምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባውን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ነው እያካሄደ የሚገኘው፡፡

በስብሰባው የምክር ቤቱን 6ኛ አመት የስራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባ ቃለ ጉባኤ መርምሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡

ከዚህ ባለፈም በተለያዩ አጀንዳዎች እንደሚመክርም ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡