ሚያዝያ 23/2013 (ዋልታ) – የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር የተለያዩ ሹመቶችን ሰጥተዋል፡፡
በዚህም መሰረት፦
1 አቶ ሰማ ጥሩነህ በም/ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሰላምና የህዝብ ደህንነት ቢሮሃላፊና የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ
2 ፡ ኮሚሽነር ተኮላ አይፎክሩ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር
3 ፡ ኮሎነል ባምላኩ አባይ በቢሮ ሃላፊ ደረጃ የአማራ ክልል ሚሊሻ ፅ/ ቤት ሃላፊ
4 ፡ አቶ ዝጋለ ገበየሁ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ
5 ፡ አቶ ሀብታሙ ሞገስ የአማራ ክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር
6 አቶ ሙሉጌታ አበራ የአማራ ክልል የፍትህ ማሰልጠኛና የህግ ምርምር ኢኒስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ሆነው መሾማቸውን ከክልሉ ኮምንኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡