ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በቱርክዬ እና ሶሪያ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የሰው ህይወት በመጥፋቱ የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

ጥር 30/2015 (ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቱርክዬ እና ሶሪያ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሰው ህይወት በመጥፋቱ የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገፃቸው ባወጡት መግለጫ በደረሰው ጉዳት ማዘናቸውን ገልጸው በአደጋ ለተጎዱትም ብርታትን ተመኝተዋል።

በደቡባዊ ቱርክዬ እና በሰሜን ሶሪያ 7.8 ሬክተር ስኬል የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የተከሰተ ሲሆን ከ4 ሺሕ 300 ሰው በላይ ህይወት ማለፉ ተገልጿል።