ባለፈው የበጀት ዓመት የተለያዩ የማዕድናት ምርቶችን በመላክ 339 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 19/2008(ዋኢማ)- ባለፈው የበጀት ዓመት በባህላዊ የማዕድን አምራቾችና በኩባንያዎች አማካኝነት  የተመረቱ  የተለየዩ  የማዕድናት  ውጤቶች  ወደ ውጭ   በመላክ  309  ሚሊዮን  ዶላር  ገቢ መገኘቱን የማዕድን ፣ ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር አስታወቀ ።

በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ባጫ ፋጂ ለዋልታ እንደገለጹት በተጠናቀቀው  የበጀት ዓመት በኩባንያዎችና በባህላዊ አምራቾች አማካኝነት በአጠቃላይ 8ሺ577 ኪሎግራም ወርቅ ፣ 8ሺ 485 ኪሎግራም ኦፓል፣  729 ሺ936 ኪ.ግ የተለያዩ  የጌጣጌጥ ማዕድናት ፣ 328.90 ሜትር ኩብ ዕብነበረድና 190.48 ቶን ታንታለም ለዓለም አቀፍ ገበያ  በማቅረብ 309  ሚሊዮን ዶላር ገቢ ሊገኝ ችሏል ።

ከማዕድን ምርቶች  አጠቃላይ ገቢ ውስጥ 138 ሚሊዮን ዶላር  የሚሆነው የተገኘው በዘመናዊ መንገድ ማዕድን  ከሚያመርቱ ኩባንያዎች ሲሆን 171  ሚሊዮን  ዶላር  የሚሆነው ከባህላዊ አምራቾች መሆኑን አቶ ባጫ ገልጸዋል ።  

በበጀት ዓመቱ በኩባንያዎችና በባህላዊ ማዕድን አምራቾች አማካኝነት 500 ሚሊዮን  ዶላር  ገቢ  ለማግኘት  ታቅዶ  ሲሠራ እንደቆየ ያብራሩት አቶ ባጫ  ከዕቅዱ  61 በመቶ የሚሆነው ገቢ ብቻ ተገኝቷል ብለዋል ።

ከዓለም የወርቅ የመግዛት ፍላጎት መቀነስ  ጋር በተያያዘ  ከወርቅ ምርት የሚገኘውን የውጭ  ምንዛሪ ለማካካስ  የተለያዩ የጌጣጌጥ  ማዕድናትን  በመላክ በዘንድሮ የበጀት ዓመት  ከማዕድን  ዘርፉ  የተሻለ ገቢ  ለማግኘት ጥረት መደረጉን አቶ ባጫ አመልክተዋል ።

በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች የሚገኙ 885 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን በበጀት ዓመቱ እንዲደራጁና የባህላዊ የወርቅና ሌሎች ማዕድናት ማምረት ሥራዎች ላይ እንዲሠማሩ በማድረግ 137 ሺ 697 የሥራ አጥ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር  ታቅዶ በበጀት ዓመቱ  738  የጥቃቅንና አነስተኛ  ኢንተርፕራይዞች ተደራጅተው 92ሺ 907 ለሚሆኑ  ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን አቶ ባጫ  አብራርተዋል ።

የማዕድን ፤ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር የአገሪቱ  ማዕድን ላኪዎች ከገዥዎቻቸው ጋር የተጠናከረ  የገበያ ትስስር  እንዲፈጥሩና ትውውቅ እንዲያደርጉ ለማስቻል በበጀት ዓመቱ ጥረት ማድረጉን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል  ዘግቧል ።  

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 19/2008(ዋኢማ)- ባለፈው የበጀት ዓመት በባህላዊ የማዕድን አምራቾችና በኩባንያዎች አማካኝነት  የተመረቱ  የተለየዩ  የማዕድናት  ውጤቶች  ወደ ውጭ   በመላክ  309  ሚሊዮን  ዶላር  ገቢ መገኘቱን የማዕድን ፣ ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር አስታወቀ ።

በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ባጫ ፋጂ ለዋልታ እንደገለጹት በተጠናቀቀው  የበጀት ዓመት በኩባንያዎችና በባህላዊ አምራቾች አማካኝነት በአጠቃላይ 8ሺ577 ኪሎግራም ወርቅ ፣ 8ሺ 485 ኪሎግራም ኦፓል፣  729 ሺ936 ኪ.ግ የተለያዩ  የጌጣጌጥ ማዕድናት ፣ 328.90 ሜትር ኩብ ዕብነበረድና 190.48 ቶን ታንታለም ለዓለም አቀፍ ገበያ  በማቅረብ 309  ሚሊዮን ዶላር ገቢ ሊገኝ ችሏል ።

ከማዕድን ምርቶች  አጠቃላይ ገቢ ውስጥ 138 ሚሊዮን ዶላር  የሚሆነው የተገኘው በዘመናዊ መንገድ ማዕድን  ከሚያመርቱ ኩባንያዎች ሲሆን 171  ሚሊዮን  ዶላር  የሚሆነው ከባህላዊ አምራቾች መሆኑን አቶ ባጫ ገልጸዋል ።  

በበጀት ዓመቱ በኩባንያዎችና በባህላዊ ማዕድን አምራቾች አማካኝነት 500 ሚሊዮን  ዶላር  ገቢ  ለማግኘት  ታቅዶ  ሲሠራ እንደቆየ ያብራሩት አቶ ባጫ  ከዕቅዱ  61 በመቶ የሚሆነው ገቢ ብቻ ተገኝቷል ብለዋል ።

ከዓለም የወርቅ የመግዛት ፍላጎት መቀነስ  ጋር በተያያዘ  ከወርቅ ምርት የሚገኘውን የውጭ  ምንዛሪ ለማካካስ  የተለያዩ የጌጣጌጥ  ማዕድናትን  በመላክ በዘንድሮ የበጀት ዓመት  ከማዕድን  ዘርፉ  የተሻለ ገቢ  ለማግኘት ጥረት መደረጉን አቶ ባጫ አመልክተዋል ።

በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች የሚገኙ 885 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን በበጀት ዓመቱ እንዲደራጁና የባህላዊ የወርቅና ሌሎች ማዕድናት ማምረት ሥራዎች ላይ እንዲሠማሩ በማድረግ 137 ሺ 697 የሥራ አጥ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር  ታቅዶ በበጀት ዓመቱ  738  የጥቃቅንና አነስተኛ  ኢንተርፕራይዞች ተደራጅተው 92ሺ 907 ለሚሆኑ  ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን አቶ ባጫ  አብራርተዋል ።

የማዕድን ፤ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር የአገሪቱ  ማዕድን ላኪዎች ከገዥዎቻቸው ጋር የተጠናከረ  የገበያ ትስስር  እንዲፈጥሩና ትውውቅ እንዲያደርጉ ለማስቻል በበጀት ዓመቱ ጥረት ማድረጉን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል  ዘግቧል ።