የአዋሽ-ኮምቦልቻ -ወልዲያ የባቡር ፕሮጀክት ግንባታ 45 በመቶ ተጠናቀቀ

ኮምቦልቻ ፤  ሐምሌ 20/2008(ዋኢማ)– በመግንባት ላይ የሚገኘው የአዋሽ – ኮምቦልቻ -ወልዲያ (ሐራ ገበያ) የባቡር ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ አፈጻጻም 45 በመቶ መጠናቀቁ  ተገለጸ።

የአዋሽ -ኮምቦልቻ-ወልዲያ(ሐራ ገበያ) የባቡር ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር  አብዱል ከሪም መሐመድ   የፕሮጀክቱን  የግንባታ  ደረጃን  ለዲያስፖራ  አበላት  ባስጎበኙበት  ወቅት እንደገለጹት ነሐሴ 2006 ዓም ግንባታው  የተጀመረው  ፕሮጀክቱ በአሁኑ  ወቅት  45  በመቶ የግንባታ ሥራው ተጠናቋል ብለዋል ።

የፕሮጀክቱን  የግንባታ ሥራ  ሙሉ  ለሙሉ  እስከ  2010 ዓም  መጨረሻ ድረስ  ለማጠናቀቅ   በአሁኑ ወቅት የግንባታው ሥራ 24 ሰዓት እየተከናወነ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ አመልክተዋል ።

የአዋሽ-ኮምቦልቻ -ወልዲያ( ሐራ ገበያ) የባቡር መሥመር በአጠቃላይ 391 ኪሎሜትር  ርቀት የሚሸፍን መሆኑን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ  የባቡር መሥመሩ ለመንገደኞችና ለእቃ ማጓጓዣነት  አገልግሎት  የሚሠጥ መሆኑን ተናግረዋል ።

የባቡሩ  መሥመሩ  የአዋሽ ፣ሐይቅ፤ ሰንበቴ፤  ካራ ቆሬ፣ ኮምቦልቻና የመርሳ  ከተሞችን  የሚያገናኝ  በመሆኑ ለአካባቢው  ለንግድ ልውውጥና ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር እንደሆነ የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ የባቡር መሥመር  ግንባታው ሲጠናቀቅ በሰዓት  120  ኪሎሜትር ያህል ይጓዛል  ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል ።

የአዋሽ – ኮምቦልቻ-ወልዲያ( ሐራ ገበያ) የባቡር ፕሮጀክት  በአጠቃላይ  በ 1ነጥብ 7  ቢሊዮን  ዶላር ወጪ  ያፒ መርክዚ   ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግ በተባለ  የቱርክ  ተቋራጭ  ኩባንያ  እየተገነባ እንደሚገኝ  ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል ።

በአጠቃላይ ፕሮጀክቱ 3ሺ500 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ዋልታ  ኢንፎርሜሽን ማዕከል  ።      

ኮምቦልቻ ፤  ሐምሌ 20/2008(ዋኢማ)– በመግንባት ላይ የሚገኘው የአዋሽ – ኮምቦልቻ -ወልዲያ (ሐራ ገበያ) የባቡር ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ አፈጻጻም 45 በመቶ መጠናቀቁ  ተገለጸ።

የአዋሽ -ኮምቦልቻ-ወልዲያ(ሐራ ገበያ) የባቡር ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር  አብዱል ከሪም መሐመድ   የፕሮጀክቱን  የግንባታ  ደረጃን  ለዲያስፖራ  አበላት  ባስጎበኙበት  ወቅት እንደገለጹት ነሐሴ 2006 ዓም ግንባታው  የተጀመረው  ፕሮጀክቱ በአሁኑ  ወቅት  45  በመቶ የግንባታ ሥራው ተጠናቋል ብለዋል ።

የፕሮጀክቱን  የግንባታ ሥራ  ሙሉ  ለሙሉ  እስከ  2010 ዓም  መጨረሻ ድረስ  ለማጠናቀቅ   በአሁኑ ወቅት የግንባታው ሥራ 24 ሰዓት እየተከናወነ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ አመልክተዋል ።

የአዋሽ-ኮምቦልቻ -ወልዲያ( ሐራ ገበያ) የባቡር መሥመር በአጠቃላይ 391 ኪሎሜትር  ርቀት የሚሸፍን መሆኑን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ  የባቡር መሥመሩ ለመንገደኞችና ለእቃ ማጓጓዣነት  አገልግሎት  የሚሠጥ መሆኑን ተናግረዋል ።

የባቡሩ  መሥመሩ  የአዋሽ ፣ሐይቅ፤ ሰንበቴ፤  ካራ ቆሬ፣ ኮምቦልቻና የመርሳ  ከተሞችን  የሚያገናኝ  በመሆኑ ለአካባቢው  ለንግድ ልውውጥና ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር እንደሆነ የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ የባቡር መሥመር  ግንባታው ሲጠናቀቅ በሰዓት  120  ኪሎሜትር ያህል ይጓዛል  ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል ።

የአዋሽ – ኮምቦልቻ-ወልዲያ( ሐራ ገበያ) የባቡር ፕሮጀክት  በአጠቃላይ  በ 1ነጥብ 7  ቢሊዮን  ዶላር ወጪ  ያፒ መርክዚ   ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግ በተባለ  የቱርክ  ተቋራጭ  ኩባንያ  እየተገነባ እንደሚገኝ  ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል ።

በአጠቃላይ ፕሮጀክቱ 3ሺ500 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ዋልታ  ኢንፎርሜሽን ማዕከል  ።