ሚኒስቴሩ በፌደራል ኦዲት መስሪያ ቤቶች ላይ የሚስተዋለውን የኦዲት ችግር ለመቅረፍ ውይይት አካሄደ

የኢፌዲሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የፌደራል ኦዲት መስሪያ ቤቶች ላይ የሚስተዋለውን የኦዲት ችግር ለመቅረፍ ከፌደራል መስሪያ ቤት ኦዲተሮች ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡

በውይይቱም 2010 በጀት ዓመት የውስጥ ኦዲት አፈፃፀም የተገመገመ ሲሆን፤ በጠንካራና ደካማ ጎን የተስተዋሉ የኢዲቲንግ ስራዎች ተነስተዋል፡፡

2009 በጀት ዓመት የዋና ኦዲት መስሪያ ቤት የጥሬ ገንዘብ ጉድለት፣ ውዝፍ ሂሳብ፣ የተከፋይ ሂሳብ ለማን እንደሚከፈል አለመታወቅ የሚሉ እና ሌሎች ግኝቶች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

በዚሁም በ112 ተቋማት 2009 በጀት ላይ በተደረገ ክትትል ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ የአላቂ እቃ ግዥ የተፈጸመና 120 ተቋማት ደግሞ ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ በአላቂ ንብረቶች ፈሰስ እንዲካተት መደረጉን ነው የተብራራው።

በዚህም ተቋማቱ በጀት ከሚቃጠል በሚል በበጀት ዓመቱ መጨረሻ አካባቢ በርካታ ስልጠናዎችና ክፍያዎችን በመፈጸም ገንዘብ የሚያባክኑ መሆኑ ተገልጿል ።

አሁን ላይ 2009 በጀት ዓመት የጎላ የኦዲት ግኝት ያለባቸው 61 ተቋማት ላይ ክትትሉ እየተደረገ መሆኑን ተጠቁሟል ፡፡

ከእነዚህም መካክል 38  ምህርት ሚኒስቴርና እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ 15 የኢኮኖሚ ልማት ዘርፎችና 13 የአስተዳደርና አገልግሎት ዘርፎች መሆናቸውም ታውቋል።

2011 የበጀት ዓመት የውስጥ ኦዲት እቅድ ላይ በጥናታዊ ፅሑፍ ተደግፈፎ ውይይት የተደረገ ሲሆን በባለፈው አመት የተስተዋለውን የኦዲት ችግር ለመቅረፍ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡

በውይይቱ ላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ኦዲት መስሪያ ቤቶች ችግሮች እንዳለባቸው የተጠቆመ ሲሆን ክትትል እና ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተሣታፊዎች አንስተዋል፡፡