የአፋር ክልል 12ኛውን የብሔር ፣ ብሐረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በድምቀት ለማክበር እየተዘጋጀ ነው

የአፋር ብሔራዊ ክልል ከሦስት  ወራት  በኋላ  ለሚያስተናግደው  12ኛው የብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን በድምቀት ለማክበር  የተለያዩ  አስፈላጊ ዝግጅቶች  እያካሄዱ  መሆኑን  አስታወቀ ።   

በክልሉ የ12ኛው የብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አስተባባሪ ኮሚቴ ኃላፊ ሞሃመድ አወል አብዱርሃማን ለዋሚኮ እንደገለጹት ከሦስት  ወራት  በኋላ የሰመራ ከተማ የምታስተናግደውን የብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች  ቀን በዓል ደማቅ  ለማድረግ  አምስት የግንባታ  ፕሮጀክቶች  እየተካሄዱ ይገኛል ።       

የክልሉ መንግሥት በዓሉን በደማቅ ሥነ ሥርዓት  ለማክበር  የተለያዩ  የመሠረተ ልማት  ግንባታ ሥራዎች  ሲከናወኑ  ቆይተዋል  ብለዋል አቶ ሞሃመድ   ።      የአፋር ክልል ከብሔር ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ጋር በተየያዘ የሁለት መንገዶች፣ የስታዲየም፣ የእንግዳ  ማረፊያ፣ ሆቴሎች፣   የመሰብሰቢያ  አዳራሽ  ግንባታዎች  እየተካሄዱ  መሆኑን አቶ ሞሃመድ ተናግረዋል   ።                      

የፌደራል መንግሥት  የሰመራን  አውሮፕላን ማረፊያ  ግንባታን ፕሮጀክትን ከብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና  ሕዝቦች  በዓል በፊት  አንዲጠናቀቅ በማድረግ የበኩሉን  አስተዋጽኦ  ማድረጉን  አቶ ሞሃመድ አመልክተዋል ።     

በአሁኑ ወቅት  እንግዶችን ያስተናግዳሉ  ተብለው  የሚጠበቁት የሆቴሎች ግንባታ ሥራ እንደ ዕቅዱም ባይሆን   በመልካም  ደረጃ ላይ እንደሚገኝ  አቶ ሞሃመድ  ተናግረዋል ።         

12ኛውን የብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና  ህዝቦች  በዓልን  በደማቅ  ሥነ ሥርዓት  ለማክበር  የፌደራል መንግሥት ፣ የፌደሬሽን  ምክር ቤትና  የበዓሉ  አስተባባሪ ኮሚቴ ተቀናጅተው  በዓሉን  ለማድመቅ እየተጉ  ይገኛል ።

11ኛው   የብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች  በዓል  በሓረር  ከተማ መካሄዱ  ይታወሳል ።