የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ አባት አረፉ
የዶክተር አብይ አህመድ አባት አቶ አህመድ አሊ ባደረባቸው ህመም በጅማ ሆስፒታል በህክምና ሲረዱ ቆይተው ነው ዛሬ ያረፉት ።
የአጋሮ ከተማ አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ባለሙያ አቶ ጌታቸው ጎዳና እንደገለጹት፤ አቶ አህመድ አሊ ወይም አባፊጣ አባናሳ ባደረባቸው ህመም በጅማ ሆስፒታል በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ አርፈዋል።
አስከሬናቸውም ዛሬ ወደ አጋሮ-በሻሻ የተወሰደ ሲሆን በነገው እለትም የቀብር ስነ-ስርዓቱ ይፈጸማል ተብሎ እንደሚጠበቅ መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።