ደረጃውን የጠበቀ የምርምር ኢንስቲትዩት ህንጻ ለመገንባት ውል ተፈረመ

የጤና ሚኒስቴር ከሀርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ጋር ደረጃውን የጠበቀ የምርምር ኢንስቲትዩት ህንጻ ለመገንባት ውል መፈራረማቸዉን ተገለፀ፡፡  

በአገሪቱ ሀገር አቀፍ የምርምር ኢንስቲትዩት የመጀመሪያ የሆነው ደረጃውን የጠበቀ እና በ 3 ዓመት ዉስጥ ተጠናቆ አገልግሎት የሚሰጥ ህንጻ ግንባታ ለማስጀመር ውል ተፈርሟል::

የጤና ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን ውሉን ከተፈራረሙ በኋላ የምርምር ተቋሙ ለአገርቱ የጤናው ዘርፍ እድገት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ይሰጠዋል ብሏል::

ኮንትራክተሩም ይህንን ከግንዛቤ በማስገባት ህንጻውን በተያዘው ጊዜ በጥራት ሰርተው እንደሚያስረክብ ያላቸውን እምነት ገልጿል::

የህንጻው ግንባታ በሚቀጥለው ሰኞ የቦታ ርክክብ ተፈጽሞ ወደ ግንባታ የሚገባ ሲሆን ለአጠቃላይ ወጪው በመንግስት 526 ሚልዮን ብር ተይዞለታል::

(ምንጭ፡- ጤና ሚኒስቴር)