ም/ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመዲናዋ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት አሠጣጥን ጎበኙ

መጋቢት 20/2013 (ዋልታ) – የአዲስ አበበ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በከተማዋ  የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት አሠጣጥን ተዘዋውረው  ጎበኙ።

አመራሮቹ ትራንስፖርት አገልግሎት  በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ነዋሪዎችን፣ ታክሲ አሽከርካሪዎችን፣ ተራ አስከባሪዎች እና የትራንስፖርት ተቆጣጣሪዎችን አነጋግረዋል።

የከተማ አስተዳደሩም  የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ችግርን ለመቅረፍ ከአውቶቡስ አቅርቦት ጀምሮ የመሰረተ ልማት እና የትራፊክ ማኔጅመንት ስራዎች ላይ በልዩ ትኩረት እየሠራ መሆኑን ከአዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሬቴሪያት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡