በችግር ውስጥ ለሚገኝ ህዝብ የመፍትሄ አካል ለመሆን ለህዝብ የቀረበ መንግስት ያስፈልጋል – ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ

መጋቢት 29/2013 (ዋልታ) – በችግር ውስጥ ለሚገኝ ህዝብ የመፍትሄ አካል ለመሆን ለህዝብ የቀረበ መንግስት እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) መሪ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ገልጸዋል፡፡

ኢዜማ ብሩህ ተስፋ ለአዲስ አበባ በሚል 138 ቁልፍ ግቦች ያላቸውን ነጥቦች ያካተተ የቃልኪዳን ሰነድ በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል፡፡

ፓርቲው በህዝብ ይሁንታ የሚመረጥ ከሆነ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ እንደሚሰራም አስታውቋል::

በፌዴራል መንግስት፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና በከተማ ምክር ቤት ከዚህ ቀደም ተቀርፀው ሲተገበሩ የነበሩ ህጎች ማሻሻያን የሚሹ መሆናቸውንም አንስቷል፡፡

ኢዜማ በዚህ ዙሪያም ማስተካከያን በማድረግ ከተማዋ ራሷን በራሷ የማስተዳደር መብቷ ሙሉ በሙሉ እንዲረጋገጥ ፓርቲው እንደሚሰራም ገልጿል፡፡

(በሄብሮን ዋልታው)