የሙሴቬኒ ተፎካካሪ ቦቢ ዋይን የምርጫ ቅስቀሳ አላደርግም አለ

የኡጋንዳ ፕሬዝዳንትዊ ምርጫ ተፎካካሪ የሆነውና በጥበብ ስሙ ቦቢ ዋይን ተብሎ የሚጠራው ሮበርት ኪያጉላኒ የምረጡኝ ዘመቻን ለማቆም እንደተገደደ ተናገረ።

ለዚህ ውሳኔ ያበቃው ደግሞ የቅስቀሳ ቡድን አባላቱ ላይ ጥቃት በመበራከቱ ነው።

ቦቢ እንደሚለው መኪናው ተሳብሮበታል፣ የቅርብ ረዳቶቹም ላይ ጥቃት ደርሶባቸዋል።

ፖሊስ ደጋፊዎቹን በመደብደብና በማሰቃየት ላይ ይገኛል።

በምሥራቅ ካምፓላ ካዩንጋ የቦቢ ደጋፊዎች አደባባይ በመውጣታቸው ፖሊስ በቆመጥና በአስለቃሽ ጭስ በትኗቸዋል።

አራት የቅስቀሳ ቡድን አባላቱም ክፉኛ ቆስለዋል ተብሏል።

ከአራቱ አንዱ የሙዚቃ ፕሮዲዩሰር የሆነው ዳን ማጂክ ሲሆን ፊቱ ላይ ጉዳት ደርሶበታል።

ቦቢ ዋይን ዛሬ ረቡዕ ወደ ምርጫ ኮሚሽን በመሄድ የምርጫ ቅስቀሳ ማድረግ ፈተና እንደሆነበት እንደሚያብራራ ለጋዜጠኞች ተናግሯል።

ምንጭ ፡- ቢቢሲ