መስከረም 13/2014 (ዋልታ) በሕግ በተደነገገው መሰረት 6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድጋሚ የሚካሄድባቸው የምርጫ ክልሎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ አደረገ፡፡
የምርጫ ክልሎቹም የሚከተሉት መሆናቸውን ቦርዱ አስታውቋል፡፡
- ባስኬቶ ልዩ – ለክልል ምክር ቤት እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
- ቡሌ – ለክልል ምክር ቤት እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
- ጉመር 2 – ለክልል ምክር ቤት
- መስቃና ማረቆ – ለክልል ምክር ቤት እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
በተጠቀሱት የምርጫ ክልሎች ድምጽ አሰጣጡ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም እንደሚከናወን ቦርዱ ጨምሮ ገልጿል፡፡