ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በ3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም መክፈቻ መርሃ ግብር ላይ ንግግር አደረጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ጥቅምት 7/2016 (አዲስ ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም መክፈቻ መርሃ ግብር ላይ ንግግር አድርገዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የቻይና-አፍሪካን ግንኙነት ጥንተ መሰረት እና እድገት አውስተው በቢአርአይ የመሰረተ ልማት ክንውን በአፍሪካ አህጉር የተጣለውን ጠንካራ የትብብር መሰረት አንስተዋል፡፡

በማደግ ላይ ያለውን የአፍሪካን ተፅእኖ የመፍጠር አቅም አፅንዖት በመስጠትም በባለብዙ ወገን መድረኮች አካታችነትን ማረጋገጥ ተገቢ እንደሆነ ማስረዳታቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡