የትግራይና አማራ ህዝቦች የጋራ ምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው

የትግራይና አማራ ክልሎች ህዝብ የጋራ ምክክር መድረክ በዛሬው ዕለት በጎንደር ከተማ መካሄድ ጀመረ ።

በምክክረ መድረኩ ላይ የሚሳተፉት 500 የሚደርሱ የትግራይ ክልል ምሁራን ፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች ፣ ወጣቶችና አመራሮች  በትናንትናው ዕለት ምሽት ወደ ጎንደር ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባባል ተደርጎላቸዋል ።

በዘሬው ዕለት  በጎንደር ከተማ በተጀመረው የምክክር መድረክ በሁለቱ ክልሎች ህዝቦች መካከል ተከስቶ የነበረውን አለመግባባት በዘላቂነት መፍታት በሚችሉባቸው ጉዳዮች  ላይ ውይይት እያደረጉ   መሆኑ  ይገኛሉ ።

የሁለቱ ክልሎች ተወካዮች ሰላምና የልማት ሂደትን በሚያረጋግጡባቸው  የጋራ ጉዳዮች ላይም  ምክክር ያካሄዳሉ ተብሎ  ይጠበቃል ።   

በትግራይና አማራ ክልል ሕዝቦች መካከል ያለመግባባትና ቅራኔ ባለፈው ዓመት መከሰቱ ይታወሳል ።   

የሁለቱ ክልሎች ህዝቦች  ባለፈው ዓመት ነሓሴ ወር መቐለ ከተማ  ላይ የጋራ ምክክር ማካሄዳቸው ይታወሳል ።