የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት /ኢጋድ/ ዋና ፀሃፊ አምባሳደር ማህቡብ ማዓሊምእናደሉት የኤርትራ ከፍተኛ የልዑክ ቡድን ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመወያየታቸው ኢጋድ እንደሚያደንቅ ገልፀዋል፡፡
ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ሁለቱ መንግስታት እና ህዝቦች መካከል ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት ዳግም መመለሱ ኢጋድን እንዳስደሰተው ተናግረዋል፡፡
አምባሳደሩ እንዳሉት ሁለቱ ሀገራት በርካታ የሚያቀራርቡ የጋራ ጉዳይ ያላቸው በመሆኑ ግንኑነታቸውን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ዳግም ማደስ እንደሚገባቸው ገልፀዋል፡፡