የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በአፍሪካ የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ለመካፈል በዛሬው ዕለት ወደ ደቡብ አፍሪካ አቀኑ ።
በደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት፣ ኢንቨስተሮች እና ሌሎች ሌሎች ተቀማት ይገኛሉ ተብሏል ።
የኢንቨስትመንት ፎረሙ በአህጉሪቱ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ይበልጥ በማስተዋወቅ ኢንቨስትመንቱ እንዲስፋፋ የበኩሉን ሚና እንደሚጫወት የሚጠበቅ ሲሆን፥ ኢትዮጵያም ያላትን የኢንቨስትመንት ዕድል ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ለመጡ ተሳታፊዎች ለማስተዋወቅ ተዘጋጅታለች ።
የአፍሪካ አንቨስትመንት ፎረም ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚካሄድ ይሆናል።
ፕሬዘዳንት ሳህለወርቅ የኢፌዴሪ ፕሬዚደንት በመሆን ከተሾሙ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ የሚያደርጉት የውጭ ሀገር ጉዞ ነው።